የኮክ አመሰራረት
የኮክ አመሰራረት
Ø በአጭር ታሪክ ኮክ ትሬዲንግ ኃ/የ/የግ/ ማኅበር አባይ ማዶ የሚገኘው የመሬቱ ባለቤቶች ሲሆኑ እነዚህን ባለቤቶች በጣምራ ዋዜማ
አፓርትመነት እና ፕላኔት አፓርትመንት ገዝተዉታል፡፡
Ø ኮክ ትሬዲንግ ኃ/የ/የግ/ ማኅበር ድርጅት መመስረት ዋነኛ ምክንያት በአባላት መካከል የበለጠ ትስስር እንዲሁም
ደግሞ ተስፋ እንዲኖር ያደረገ የመፍትሔ ሃሳብ ነበር፤ይህም በ2012 ተከስቶ የነበረው የኮሮና ቫይረስ የአክሲዮናችን አባላት ተስፋ
የቆረጡበት እና በካፒታል ደረጃም እዚህ ግባ የማይባል በእያንዳንዱ ሽር 6,000 ብር ( ስድስት ሽህ ብር ) የተዋጣ እና በድምሩ 3.5 ሚሊዮን ብር የደረሰ
ነበር ፡፡ በዚህም እህት ኩባንያ ከሆነው ፕላኔት አፓርትመንት ጋር በተመሳሳይ የሃብት መጠን የነበረ ሲሆን በዚህም ከ አጋር የዳይሬክተሮች
ቦርድ ጋር በመግባባት ፒኢልሲ /ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኃበር /
በሃገራችን የንግድ ህግ በሚደነግገው ለባለቤትነት የሚያበቃ ሁለት እና ከዚያ በላይ ሰዎች ስለሚፈቅድ በጋራ ዋዜማ እና ፕላኔት አፓርትመንት 50% ፣50% በመያዝ 5000 ካ.ሜ ቦታ በ 8,000,000 /ስምንት ሚሊዮን ብር/ መግዛት ተችሏል፡፡
በእርግጥም መሬት፤ የሰዉ ልጅ በደም ዝምድና እንደሚስተሳስር ሁሉ መሬትም ያስተሳስራል፤ ተስፋ ፈነጠቀ፣ራዕይ ታወቀ፣ ብዙ ዓመታትን በተስፋ አሳለፍን፤ወደፊትም ቀጥሎ ሃሳባችንን እዉን ለማድረግ ፣ያቀድነውን ግንባታ ገንብቶ ለማጠናቀቅ ጊዜውን ተለምነናል፡፡