×
Socials
Wazema Facebook Wazema Telegram Planet Telegram Planet Facebook

Our Story

የኮክ አመሰራረት

የኮክ አመሰራረት

Ø  በአጭር ታሪክ ኮክ ትሬዲንግ ኃ/የ/የግ/ ማኅበር  አባይ ማዶ የሚገኘው የመሬቱ ባለቤቶች ሲሆኑ እነዚህን ባለቤቶች በጣምራ ዋዜማ አፓርትመነት እና ፕላኔት አፓርትመንት ገዝተዉታል፡፡

Ø  ኮክ ትሬዲንግ ኃ/የ/የግ/ ማኅበር  ድርጅት መመስረት ዋነኛ ምክንያት በአባላት መካከል የበለጠ ትስስር እንዲሁም ደግሞ ተስፋ እንዲኖር ያደረገ የመፍትሔ ሃሳብ ነበር፤ይህም በ2012 ተከስቶ የነበረው የኮሮና ቫይረስ የአክሲዮናችን አባላት ተስፋ የቆረጡበት እና በካፒታል ደረጃም እዚህ ግባ የማይባል በእያንዳንዱ ሽር 6,000  ብር ( ስድስት ሽህ ብር ) የተዋጣ እና በድምሩ 3.5 ሚሊዮን ብር የደረሰ ነበር ፡፡ በዚህም እህት ኩባንያ ከሆነው ፕላኔት አፓርትመንት ጋር በተመሳሳይ የሃብት መጠን የነበረ ሲሆን በዚህም ከ አጋር የዳይሬክተሮች ቦርድ ጋር በመግባባት  ፒኢልሲ /ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኃበር / በሃገራችን የንግድ ህግ በሚደነግገው  ለባለቤትነት የሚያበቃ  ሁለት እና ከዚያ በላይ ሰዎች ስለሚፈቅድ በጋራ ዋዜማ እና ፕላኔት አፓርትመንት  50% ፣50% በመያዝ 5000 ካ.ሜ  ቦታ በ 8,000,000 /ስምንት ሚሊዮን ብር/ መግዛት ተችሏል፡፡

በእርግጥም  መሬት፤ የሰዉ ልጅ በደም ዝምድና እንደሚስተሳስር ሁሉ መሬትም  ያስተሳስራል፤ ተስፋ ፈነጠቀ፣ራዕይ ታወቀ፣ ብዙ ዓመታትን በተስፋ አሳለፍን፤ወደፊትም ቀጥሎ ሃሳባችንን እዉን ለማድረግ ፣ያቀድነውን ግንባታ  ገንብቶ ለማጠናቀቅ ጊዜውን ተለምነናል፡፡      

የነበረበት ሁኔታ

የነበረበት ሁኔታ

የአክሲዮን እሳቤ የጥቂት ግለሰቦች መበልፀጊያ እና መጠቀሚያ፤ እንዲሁም በካፒታል ደረጃ ማለትም ጠንካራ የገንዘብ አቅም ያላቸው ግለሰቦች የሚያንቀሳቅሱት በሚል ሃሳብ የተቀመጠውን እሳቤ የሻረ ሁኖ ወደ አዲስ አስተሳሰብ መምጣት የተቻለበት፤ከቁጠባ ወደ ኢንበስትመንት የተሸጋገርንበት፣በቢሮ ደረጃ የዕለት ከዕለት ተግባር ሁኖ ለሌሎችም አርአያ የሆንንበት፣የፍይናንስ ግልፀኝነት በተለይም በማስታወሻ ደብተር አትሞ ግልፅ ማድረግ፣ ዘመን ተሸጋሪ ራዕይ  ወ.ዘ.ተ ያልነበሩትን ሁኔታዎች ቀርፎ  ለሌሎችም አርአያ የሆንንበት ነው፡፡ ነገር ግን በፈተናዎች አልፈን ለምናስበው እቅድ ወደፊት ያሰብንበት ግን ሊዘነጉ የማይቻሉ ሁነው አልፈዋል፡፡